Medical

የሕክምና ዋስትና ተጠቃሚ ግለሰቦች ሊገነዘቡዋቸው የሚቡ ዋና ዋና ነጥቦች

ታካሚው የካሣ ክፍያ ጥያቄ በሚያቀርቡበት ጊዜ የሚከተሉት ሰነዶችና ደረሰኞች መሟላት አለባቸው፣

  1. የህክምና ማስረጃዎች ህክምና አቅራቢው ከተመረመሩበት ቀን ጀመሮ በዘጠና ቀናት ውስጥ ለድርጅችን መቅረብ ይገባዋል፡፡
  2. በህክምና ካሣ ጥያቄ ማቅረቢያው ቅጽ ላይ ካሚው ወይም የሚመለተው ክፍል በመሙላች መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ታካሚው የበሽውን ዓይነትና የተመረመረበትን ቀን የማገልጽ የህክምና የምስክር ወረቀት ከከመበት ጤና ማዕከል ወይመ ተቋም ማቅረብ፣ /ሠርተፊኬት/
  4. በህክምና ምስክር ወረቀት መሠት የመድኃኒቶችን ማዘዣ ማያያዝ /ኘሪስክሪኘሽን/
  5. የምርመራው፣ የላቦራቶና ሌሎች የህክምና ወጪዎች የዋጋ ደረሰኞች የምርመራ ዓይነትና የተደረገ ወጪ በዝርዝር
  6. የመድኃነት ግዥ ደረሰኞች በመድኃኒት ማዘዣው መሠት የመድኃኒቱን ዓይነት፣ መጠንና ዋጋ በዝርዝር የሚገልጽ ደረሰኝ ማቅረብ፣

ማሳሰቢያ:

  1. . መድኃኒት መገዛት ያለበት ህጋዊ ፈቃድ ካላቸው መድኃኒት ቤቶች ሲሆን ለድንገተኛ ህክምና ካልሆነ በስተቀር በክሊኒኮች ውስጥ መድኃኒት መግዛት ክልክል ነው፡፡
  2.  አንዳንድ የላቦራቶና ተዛማጅ ምርመራዎች ሕክምና በሚደረግበት ክሊኒክ ውስጥ የማይሰጡ ከሆኑና በሌላ ክሊኒክ ወይም የጤና ማዕከል ምርመራዎቹን ማድረግ ካሰፈለገ ምርመራዎቹ በሐኪሙ ስለመዘዛቸው የሚገልጽ ማዘዣ መያያዝ አለበት፡፡
  3. ተጨማሪ ማስረጃ ወየም ሰነድ እንደአስፈላጊነቱሊጠየቁ ይችላሉ፡፡